አቶ አያሌው ጌታነህ የመገናኛ ብዙኃን ማስፋፊያ የሥራ ሂደት ዳይሬክተር በዓሉን በንግግር ሲከፍቱ "ሴቶችእንደሚታወቀውየሕብረተሰቡግማሽአካልናቸው፡፡በመሆኑምሊከበሩ፣ሊወደዱናሊፈቀሩይገባል፡፡እርግጥነውከዚህበፊትብዙየባህልናየኢኮኖሚተፅዕኖይደረግባቸውነበር፡፡ይሁንእንጂባካሄዱትጠንካራትግልበርካታድሎችንእየተጐናፀፉመጥተዋል፡፡"ብለዋል፡፡
ወ/ሮ ዱሬቲ ታደሰ እና ወ/ሪት መታገስ ሳሙኤል በተከታታይ የባለስልጣኑ ባለሙያዎችና የግብረ ኃይሉ አስተባባሪዎች የሴቶችን ሀገር አቀፍ እና ዓለም ዓቀፍ እንቅስቃሴ አስመልክተው ፅሁፍ አቅርበዋል፡፡ ማርች 8 በተባበሩት መንግስታት ዕውቅና አግኝቶ እንዲከበር ከተደረገበት ቀን ጀምሮ ሀገራት ቀኑን ብሔራዊ በዓል በማድረግ በልዩ ልዩ ዝግጅት ድንበር፣ ዘር፣ ቋንቋ፣ ባህል፣ ኃይማኖት፣ ኢኮኖሚና ፖለቲካ ሳይለያቸው በጋራ እያከበሩት ይገኛሉ፡፡ በመሆኑም እኛም በዓሉን በዛሬው ዕለት በዚህ መልኩ ተሰባስበን በድምቀት በማክበራችን የተሰማን ደስታ እጥፍ ድርብ ነው ብለዋል፡፡
በዓሉን በባለሙያዎች የቀረቡ አዝናኝና ቁምነገር አዘል ግጥሞች እንዲሁም በሴቶችና በባለስልጣኑ ዙሪያ ያጠነጠኑ የጥያቄና መልስ ውድድሮች ያደመቁት ሲሆን ለተወዳዳሪዎችም በሚያምሩ የስጦታ ወረቀት የተጠቀለሉ ትንሽ የሚመስሉ ነገር ግን አጓጊ ሽልማቶች ተበርክቷል፡፡
በድምቀት የተጀመረው በዓል ሲጠናቀቅ አቶ ልዑል ገብሩ የኢንፎርሜሽንና ሕዝብ ግንኙነት የሥራ ሂደት ዳይሬክተር፡ "ዛሬ ብዙ ቁምነገር አግኝተናል፡፡ ዋናው ነገር ሴቶችን ማብቃት ነው፡፡ ሴቶች ከበቁ ደግሞ የ5ቱን ዓመት የዕድገትና የትራንስፎርማሽን ዕቅድ ያለጥርጥር እናሳካለን፡፡ በመሆኑም ሁላችንም እንደአንድ ሠራዊት፣ እንደ አንድ ተቋም ባለደረቦች በጋራ ለጋራ ዓላማ እንረባረብ፡፡" ብለዋል፡፡
ማርች 8 በሀገራችን ለ35ኛ ጊዜ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ100ኛ ጊዜ መከበሩ ታውቋል፡፡ |