|
|
|
ሴት ባለሙያዎቻችን ዱብ ዱብ አሉ፡፡
የሩጫው መሪ ቃል «የቤተሰብ ምጣኔ በምርጫ »የሚል ነበር፡፡ መጋቢት 5 ቀን 2003 ዓ.ም |
መጋቢት 4 ቀን 2003 ዓ.ም ማርች 8 ምክንያት በማድረግ ለስምንተኛ ጊዜ በተዘጋጀው የሴቶች ታላቁ ሩጫ ላይ የባለስልጣኑ ሴት ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆኑ፡፡ውድድሩም በጣም የደመቀና ያማረ ነበር፡፡
ውድድሩ ከመጀመሩ ቀደም ብሎ የባለስልጣኑ ሴት ባለሙያዎች ከጠዋቱ 1፡30 ላይ በባለስልጣኑ መ/ቤት ተገኙ፡፡ የባለስልጣኑን ሎጎ ቲሸርቱ ጀርባ ላይ በማድረግ ተቋሙን የማስተዋወቅ ስራ ሰሩ፡፡
ባለሙያዎቹ መነሻቸውን ብሮድካስት በማድረግ አትላስ ሆቴል ድረስ ሰውነታቸውን እያሟሟቁ የሮጡ ሲሆን አትላስ ከደረሱ በኋላ ከታዋቂ አርቲስት ቻቺ ታደሰ ጋር በመሆን ቀለል ያሉ ኤሮቢክስ እስፖርቶችን በመስራት ወደ ውድሩ ውስጥ ገብተዋል፡፡
|
ባለሙያዎቹ ሩጫውን ባጠናቀቁበት ወቅት
|
ውድድሩን ታዋቂዎቹ አትሌቶች ሻለቃ ሓይሌ ገ/ስላሴና መሰረት ደፋር ያስጀመሩ ሲሆን ተይዞ የነበረው ረከርድም መሰበሩ ታውቋል፡፡
በውድድሩ ላይ ዘጠኝ ሺህ የሚደርሱ ተወዳዳሪዎች የተሳተፉ ሲሆን የባለስልጣኑም ሴት ባለሙያዎች በውድድሩ እንደተደሰቱ ገልጸዋል፡፡ ለሩጫው ሶስት አይነት ሜዳሊያ የተዘጋጀ ሲሆን ከ1-3ኛ ደረጃ ለወጡ በሽልማትነት ተሰጥቷል፡፡ በመጨረሻም የፎቶ መነሳት ፕሮግራም ተካሂዶ የውድድሩ ፍጻሜ ሆኗል፡፡ |
|
|
Updated September 2009 Copyright © 2009
Ethiopian Broadcasting Authority. All righs
reserved.
|
You Are Visitor Number
|
|
|
|
|