....... .. . . ............................... ......
የባለሥልጣኑ አዲስ ሎጎ ያለበትና 59 ገጾችን በሁለት ክፍል አካቶ የያዘው ይኸው ቡክሌት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር የታተመ ሲሆን ቡክሌቱ በተቋሙ የኢንፎርሜሽንና ሕዝብ ግንኙነት የሥራ ሂደት በመሰራጨት ላይ ይገኛል፡፡
ክፍል አንድ በባለሥልጣን መ/ቤቱ በ2002 የተደረገውን ሀገር አቀፍ ጠቅላላ ምርጫን መሠረት በማድረግ ያደረገውን የመገናኛ ብዙኃን ነፃ የአየር ሰዓትና የጋዜጣ አምድ ድልድልና አጠቃቀም አስመልክቶ ያከናወናቸውን ሥራዎች የሚዘረዝር ሲሆን ክፍል ሁለት ባለስልጣን መ/ቤቱ ከምርጫ ሥራ ጎን ለጎን በበጀት ዓመቱ ያከናወናቸውን ሌሎች ሥራዎችን ይቃኛል፡፡
በባለሥልጣኑ የኢንፎርሜሽንና ሕዝብ ግንኙነት የሥራ ሂደት ዳይሬክተር አቶ ልዑል ገብሩ ቡክሌቱ በዓይነቱ የመጀመሪያ መሆኑን ጠቁመው በአራተኛው አገር አቀፍ ጠቅላላ ምርጫ ተሳትፎ ላደረጉና ለፖለቲካ ፓርቲዎች ነፃ የአየር ጊዜና የጋዜጣ አምድ በመመደብ ዓላማቸውንና ፕሮግራማቸውን እንዲያስተዋውቁ ከፍተኛ ጥረት ላደረጉት የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እንዲሁም ለተለያዩ ባለድርሻ አካላት ቡክሌቱ እንደሚሰራጭ ጠቁመዋል፡፡
ቡክሌቱ በሽፋኑ የውስጥ ገጾች የባለስልጣኑና የምርጫ ቦርድን ራዕዮች፣ ተልዕኮዎች እና እሴቶች አካቷል፡፡
ቡክሌቱ በምርጫ ወቅት የነበረውን ነፃ የአየር ሰዓትና የጋዜጣ አምድ አጠቃቀም ሁኔታ በስፋት የሚዳስስና በቀጣይ መደረግ ስላለባቸው ቁምነሮች በስፋት የሚጠቁም በመሆኑ ባለድርሻ አካላት ለተለያዩ ጥናትና ምርምር ሥራዎች ቢጠቀሙበት አስተዋጽኦው የጐላ እንደሆነ ዳይሬክተሩ ጠቅሰዋል፡፡
ቡክሌቱን በSoft Copy ከባለስልጣኑ መ/ቤት ማግኘት የሚችሉ ሲሆን በተጨማሪም በባለስልጣኑ ድረ ገጽ www.eba.gov.et ላይ የሚጫን በመሆኑ በቀላሉ Down Load አድርጎ መጠቀም እንደሚቻል ተገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ ብሮድካሥት ባለስልጣንና የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ጽ/ቤት በምርጫ ነፃ የአየር ጊዜና የጋዜጣ አምድ አጠቃቀም ዙሪያ በጋራ ተባብረው ሲሰሩ መቆየታቸው ይታወቃል፡፡