Banner
yfÝDÂ MZgÆ                              QòC
yÞZB /ymNGST ÊD× fÝD
yÞZB /ymNGST t½l¤vþiN fÝD
y¥HbrsB ÊD× fÝD
    የውጪ የብሮድካስት ፕሮግራሞችን ለደንበኞች በክፍያ የማድረስ አገልግሎት ለተጨማሪ ቻናል የፈቃድ ማመልከቻ ቅጽ
    የንግድ ሬድዮ የፈቃድ ማመልከቻ ቅጽ
    yWÀ yBéDµST PéG‰äCN tqBlÖ bKFà ldNb®C y¥DrS xgLGlÖT fÝD
    bygþz¤W y¸wÈ HTmT MZgÆ
  የማስታወቂያ ቅሬታና ጥቆማ ቅፅ
    በብሮድካስት አገልግሎት ላይ የሚቀርብ ቅሬታ ማመልከቻ ቅጽ
*     *     *     *     *    *
bygþz¤W y¸nsù _Ãq½ãC
yz¤Â KMCT(NEWSArchive)
yp½ÊÄþµL KMCT(Perdical Archive)
 
«Ý¸ DrgòC
ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን
መገናኛና ኢንፎርማሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስተር
የኢትዮያ ሰብአዊመብት ኮሚሽን
ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ
ጤና ጥበቃ ሚኒስተር
የህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም
የህዝብ ተወካዮች ፅ/ቤት
ኢትዮ ቴሌኮም
የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን
የከፍተኛ ት/ት አግባብነት ጥራት ኤጀንሲ
አዲስ አበባ ወጣቶች መሀበር
አዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ም/ቤት
ስነምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን
xþÊt½D
êL¬
yBéDµStéC xD‰š
 
 
 yx¥R¾ ðd§T GDfT y¸ÃU_ä kçn update internet explorer 8

z¤Â

ባለስልጣን መ/ቤቱ ለባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን በ2005 ዓ/ም በጀት ዓመት ከያዛቸው የአቅም ግንባታ ፕሮግራሞች መካከል አንዱ ለተቋሙ ባለሙያዎች በወቅታዊና አገራዊ ጉዳዮች ላይ ስልጠና መስጠት ነው፡፡
በዚህም መሰረት ከግንቦት 7 እስከ 17 ቀን 2005 ዓ/ም የሚቆይ ለ9 ተከታታይ ቀናት የመጀመሪያ ዙር ስልጠና በባለስልጣኑ መሰብሰቢያ አዳራሽ መስጠት ጀምሯል፡፡ የተቋሙ የሰው ሃብት አመራርና ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዘውዱ አድማስ በስልጠናውን መከፈቻ ላይ እንደተናገሩት የስልጠናው ዓላማ የተቋሙ ባለሙያዎች በኢትዮጵያ ህዳሴና በሌሎች አገራዊ ጉዳዮች የጠለቀ ግንዛቤ ኖሯቸው ከሚሰሩት ሥራ ጋር ተጨባጭ በማድረግ ያላቸውን የአቅም ክፍተት ለመሙላት እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

desta tesfaw

አቶ ዘውዱ የመክፈቻ ንግግር ሲያደርጉ   ስልጠናው ተሳታፊዎች በጥቂቱ

ስልጠናውም በዋናነት የሚያተኩረው የኢትዮጵያ ህዳሴ መሰረታዊ ጉዳዮች፣ የአምስት ዓመቱ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የሁለት ዓመት ተኩል አፈጻጸምና የቀጣይ አቅጣጫዎች፣ በኢትዮጵያ ህዳሴ ጉዞ የሚዲያ ሚና፣ የመገናኛ ብዙኃን ህጋዊ ማዕቀፎች እንዲሁም የለውጥ ሰራዊት ግንባታ በተቋሙ ያለበት ደረጃ በሚሉት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ነው፡፡
ስልጠናውም በ2 ዙን የሚሰጥ ሲሆን የመጀመሪያው ዙር ስልጠና ከግንቦት 07 ቀን 2005 ዓ/ም ጀምሮ በመሰጠት ላይ ይገኛል፡፡

ኤች አይ ቪ/ኤድስ የተመለከቱ ጉዳዮችን በመደበኛ ሥራ አካቶ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ተገለጸ!

ኤች አይቪ የመከላከያና የመቆጣጠሪያ ሥራዎችን በተቋሙ ዋና ዕቅድ ላይ እንደአንዱ ተግባር በመመልከት አካቶ ተግባራዊ ማድረግ በሚቻልበት መንዶች ላይ ስልጠና ተሰጠ፡፡

የባለሥጣን መ/ቤቱ የሴቶች፣ሕጻናትና ወጣቶች ጉዳይ ማስተባበሪያ ከብሔራዊ የኤች አይ ቪ መከላከያና መቆጣጠሪያ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ኤች አይ ቪ/ኤድስ የሚመለከቱ ተግባራትን በመደበኛ ሥራዎች ላይ እንዴት አካቶ መሥራት እንደሚገባ ለባለሥልን መ/ቤቱ የሥራ ክፍል ኃላፊዎችና የቡድን መሪዎች ግንቦት 1 ቀን 2005 ዓ/ም በተሰጠው ስልጠና ላይ ተገልጿል፡፡

desta tesfaw

 

ጽ/ቤቱን በመወከል ስልጠና የሰጡት አቶ በቀለ ደለለኝ ሲሆኑ የበሽታው ስርጭት አሁንም አሳሳቢ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ በተለይ በማደግ ላይ የሚገኙ አገሮች ላይ ችግሩ ጎልቶ የሚታይ እንደሆነ የገለጹት ተወካዩ፤ በአገራችንም ይኸው ሁኔታ በስፋት የሚስተዋልበት ሁኔታዎች እንዳሉ አስረድተዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት 34 ሚሊዮን ከቫይረሱ ጋር የሚኖሩ ሰዎች እንዳሉ የጠቆሙት ተወካዩ አብዛኛው ወይን ከ22 ሚሊዮን ባለይ ወይም 67 ከመቶው የሚገኘው ከሰሐራ በረሀ በታች በሚገኙ ታዳጊ አገሮች ይገኛሉ፡፡ በአገራችን ደግሞ ከ7 መቶ 50ሺ በላይ ሰዎች ከቫይረሱ ጋር ይኖራሉ፡፡ ይህ ቁጥር ወላጅ አልባ የሆኑትን ሕጻናትና ጧሪ ያጡ አረጋውያንን ሳይጨምር ነው፡፡ ከዚህ ምንረዳው በሽታው አሁንም አሳሳቢነቱ እንደቀጠለና ለአንዳ አፍታ የምንዘናጋበትን ሁኔታ ውስጥ እንደሌለን ገልጸዋል፡፡
ከዚህ አንጻር ተቋማት የበሽታውን ስርጭት ከመግታትና ከመቆጣር አንጻር በርካታ ሥራዎች አሉባቸው፡፡ ይህውም የኤች አይቪ /ኤድስ  የሚመለከቱ ሥራዎችን በመደበኛ ዕቅዶቻቸው በማካተተት የዕለት ተዕለት ተግባራቸው ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡ በተቋም ደረጃ ኤች አይ ቪን ዋና ተግባር ከማድረግ አስቀድሞ የሁኔታ ዳሰሳ ጥናት ማድረግ እና በተቋሙ ያሉትን አዎንታዊ ሁኔታዎች አጠናክሮ መሆድ አንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
የተቋሙ የሴቶች፣ሕጻናትና ወጣቶች ጉዳይ ማስተባበሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ዱሬታ ታደሰ እንደተናገሩት ኤች አይ ቪን በተመለከተ የአደጋ ተጋላጭነት ጥናት ለማከናወን በሂደት ላይ መሆኑን ጠቁመው የሥራ ክፍሎችም ጉዳዩን በሚገባ በመረዳትና በማስረዳት የዕቅድ አካል ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ ለዚህ ስኬት ማስተባበሪያው ከተቋሙ የውስጥ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀኛጅቶ ይሠራል ብለዋል፡፡

በቀረቡት ጉዳዮች ላይ ጥያቄዎችና አስተያቶች ከተሳታፊዎች ተነስተው በጽ/ቤቱ ተወካይ መስል ተሰጥተዋቸዋል፡፡

በመገናኛ ብዙኃን ላይ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችል ስልጠና እየሰጠ መሆኑ ባለሥልጣን መ/ቤቱ አስታወቀ!

በአገሪቱ ውስጥ የሚገኙ የመገናኛ ብዙኃን ውጤቶች ላይ የሚታዩ ችግሮች ለመቅረፍ የሚያስችል ተከታታይ የሆነ የአቅም ግንባታ ስልጠና እየሰጠ እንደሆነ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን አስታወቀ፡፡ ከተለያዩ የብሮድካስት አገልግሎት እና የሕትመት ውጤቶች ለተውጣጡ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ከሚያዝያ 17-19 ቀን 2005 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሆቴል ስልጠና ተሰጠ፡፡
የተቋሙ የመገናኛ ብዙኃን የክትትልና ዓቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ደሬሳ ተረፈ ስልጠናውን ሲከፍቱ እንደተናገሩት መ/ቤቱ በመገናኛ ብዙኃን ዘርፍ ለመሠማራት ለሚፈልጉ አካላት የፈቃድ፣ የምዝገባና የብቃት ማረጋገጫ ከመስጠት ባሻገር በዘርፉ የሚታዩትን ችግሮችን ለመቅረፍ የክትትልና የአቅም ግንባታ ሥራዎች ያከናውናል ብለዋል፡፡ በመሆኑም የተጀመሩትን የአቅም ግንባታ ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ለማስቻል ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅርበት እየሠራ መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል፡፡ 
ሰልጣኞች በስልጠናው የሚያገኙት አቅምና ተሞክሮ ተጠቅመው በየአካባቢያቸው የተጀመሩት የልማትና የዴሞክራሲ ግንባታ ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ለማድረግ ትልቅ ኃላፊነት እንደሚጠበቅባቸው አቶ ደሬሳ አስገንዝበዋል፡፡
የባለሥልጣን መ/ቤቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ደስታ ተስፋው በበኩላቸው “የኢትዮጵያ ህዳሴና የሚዲያ ሚና” የሚል የመወያያ ጽሑፍ ሲያቀርቡ እንደተናገሩት መገናኛ ብዙኃን ልማትን በማፋጠን፣ ዲሞክራሲያዊ ስርአት በመገንባት እና መልካም አስተዳደርን በማስፈን ጉልህ ድርሻ አላቸው፡፡ መንግሥት የያዘውን የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ያለመገናኛ ብዙኃን ድጋፍና እገዛ ግቡን እንደማይመታ ገልጸዋል፡፡
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና የኮሙዩኒኬሽን ፋካሊቲ ረዳት ፕሮፌሰርና ኢንስትራክተር ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ በበኩላቸው “ልማታዊና ዴሞክራሲያዊ ሚዲያ”  የሚል ጽሑፍ ሲያቀርቡ እንደተናገሩት በአገሪቱ የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ከተፈለገ ልማታዊ የጋዜጠኝነት ሥራ በተቀናጀና በተደራጀ መልኩ መሠራት እንዳለበት ገልጸዋል፡፡

desta tesfaw

ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ ስልጠናውን ሲሰጡ

እንደ ረዳት ፕሮፌሰሩ ገለጻ ልማታዊ ጋዜጠኛ የስኬት ታሪኮችን ብቻ መዘገብ ሳይሆን አንድ ፕሮጀክት ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ድረስ የነበሩ ተሞክሮዎችንና በወቅቱ ያጋጠሙ ችግሮችን በመለየት ለቀጣይ መሰል ተግባር ትምህርት በሚሰጥ መልኩ ተቃኝቶ መቅረብ አለበት ብለዋል፡፡
አንዳንድ የስልጠናው ተሳታፊዎች እንደገለጹት ተቋሙ መገናኛ ብዙኃንን ለመደገፍና ለማስፋፋት እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ የሚደነቅ ነው፡፡ ነገር ግን ዘርፉ የሚጠበቅበት ያህል የመሪነት ሚና እንዳይጫወት በመረጃ አቅርቦት ላይ የሚታዩ እጥረቶች፣ ሁሉም ሚዲያዎች ተቀራርበውና ተደጋግፈው አለመሥራታቸው እና የተወሰኑ ሚዲያዎች በአገራዊ ጉዳዮች ላይ ወጥ የሆነ አገራዊ አጀንዳ ያለመያዝ በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቶት መሠራት እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡
በስልጠናው ላይ ከመንግሥት/ሕዝብ፣ ከንግድና ከማኅበረሰብ ብሮድካስት አገልግሎት፣ ከመንግሥትና ከግል ሕትመት ውጤቶች፣ ከብዙሃን ማሕበራት፣ ከፖሊስ ኮምሽን የተውጣጡ 26 የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን፣ የመገናኛ ብዙኃንና የሕግ ማእቀፍ፣ ልማታዊና ዴሚክራሲያዊ ሚዲያ አስፈላጊነት በኢትዮጵያ፣ የኢትዮጵያ ሕዳሴና የሚዲያ ሚና እነዲሁም የመገናኛ ብዙሃን ክትትል ግኝቶች የሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ቀርበዋል፡፡

Updated September 2009 Copyright © 2009
Ethiopian Broadcasting Authority. All righs reserved.
You Are Visitor Number
votech college
like this


ENGLISH PAGE
ዜና መፅሔት ሚያዚያ 2005
አዲስ የወጣ የማህበረሰብ ሬድዮ መመሪያ
ሙሉውን መመሪያ pdf ይመልከቱ
የስልጠናና የውይይት ሰነዶች
ለብሮድካስተሮችና ለባለድርሻ አካላት ለውይይት የተዘጋጀ ሰነድ(.ppt)
የልማታዊ ጋዜጠኝነት አስፈላጊነት በኢትዮጵያ(.ppt)
የጋዜጠኝነት ስነምግባርና መልካም አተገባበር(.ppt)
አዲስ የወጡ መመሪያዎች   
    >የመንግስት ወይም የህዝብ ብሮድካስት አገልግሎት ፍቃድ አሰጣጥ መመሪያ ቁጥር 1/2003
    >የብሮድካስት አገልግሎት ፕሮግራም ቅጂ አያያዝ መመሪያ ቁጥር 2/2003
    >የመገናኛ ብዙሀን እና ተያያዥ የንግድ ስራ መደቦች የሞያ ብቃት ማረጋገጫ መስፈርቶችንነ ለመወሰን የወጣ መመሪያ ቁጥር 3/2003
Bé¹R
ፈቃድ የወሰዱ የማኅበረሰብ ሬዲዮ
ብሮድካስት አገልግሎት ጣቢያዎች
ዝርዝር መረጃ
የማኅበረሰብ ሬዲዮ ብሮድካስት
አገልግሎት
የብሮድካስትአገልግሎት ፈቃድ
ለማግኘት መሟላት ያለባቸው ቅድመ
ሁኔታዎች
በብሮድካስተሮች ላይ ስለሚቀርቡቅሬታዎችና ጥቆማዎች
በየጊዜው የሚወጣ
የሕትመት ምዝገባ እንዴት ይካሄዳል?
የኢትዮጵያ
ብሮድካስት ባለሥልጣ ን አጠቃላይ
መረጃ
በመገናኛ ብዙሃን አማካይነት የሚፈጸም ወንጀል የሚያስከትለው ኃላፊነት
በማስታወቂያ ሥራ ለመሰማራት የሙያ ብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ለማግኘት የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎች
የመገናኛ ብዙኃን እና ተያያዥ የንግድ ሥራ መደቦች የሙያ ብቃት ማረጋገጫ መስፈርቶች

 

 

 
z¤Â mIÿT
xm¬êE mI¼¤T
PÊS ¶lþZ
æè Ul¶